ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለቅጣት ተቃርቧል! የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ምሽት 4:45 ሰዓት ከዴንማርክ አቻው ጋር የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታውን ያደርጋል። በጨዋታው የብሔራዊ ቡድኑ አምበል ክርስቲያኖ ሮናልዶ በአሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ አሰላለፍ ውስጥ እንደሚካተት ይጠበቃል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ በዛሬው ጨዋታ የማስጠንቀቂያ ካርድ የሚመለከት ከሆነ ፖርቹጋል ላይ የሚደረገው የመልስ ጨዋታ በቅጣት የሚያመልጠው ይሆናል። ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ስለ ሮናልዶ በሰጡት አስተያየት “በቡድኑ ውስጥ ሮናልዶ ስላለ ደስተኛ ነኝ የቡድኑን ደረጃ እና አብሮነት ያሳድጋል “ ብለዋል።