ማንችስተር ዩናይትድ የዎልቭሱን አጥቂ ማቲውስ ኩንሃን ለማስፈረም ቀደም ሲል ንግግር መጀመሩ ይታወሳል። አሁን ባለው መረጃ መሰረት ቀያዮቹ ሰይጣኖች የዚህን ተጫዋች ዝውውር በተቻለ ፍጥነት ለማጠናቀቅ በከፍተኛ ሁኔታ እየሰሩ ይገኛሉ።
በተጨማሪም አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ይህን ተጫዋች ወደ ቡድናቸው ለማምጣት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው ተገልጿል። በራሱ በኩል ማቲውስ ኩንሃ ማንችስተር ዩናይትድን ለመቀላቀል ፍላጎት እንዳለው ምንጮች ይጠቁማሉ።
በአጠቃላይ ማንችስተር ዩናይትድ ይህንን ዝውውር ለማሳካት የሚያደርገው ጥረት በአሁኑ ሰዓት በተሳካ መንገድ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል።