19.3 C
London
Saturday, August 2, 2025

የቦዶ ተጫዋቾች ቶተንሀምን ከኖርዌይ ቡድኖች ጋር አመሳሰሉ፤ ፖስቴኮግሉ ምላሽ ለመስጠት ቃል ገቡ

የኖርዌዩ ክለብ ቦዶ ግሊምት ተጫዋቾች ከመጀመሪያው ዙር ጨዋታ በኋላ በሀገራቸው ለሚሰራጭ ጋዜጣ ቶተንሀምን “ደካማ ቡድን ነው” በማለት መተቸታቸው ተዘግቧል።

የክለቡ ተከላካይ ፍሬድሪክ ሾቮልድ “ቶተንሀም የሚፈጥረው ጫና በቀላሉ የሚቆም ነው፤ ተጫዋቾቻቸው በቀላሉ ይወድቃሉ። በአጠቃላይ ከኖርዌይ ሊግ ቡድኖች የተሻሉ አይደሉም” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።

ሌላው የቡድኑ ተጫዋች አንድሬ ጆርካን በበኩሉ “የተሸነፍነው በቡድኑ ጫና ሳይሆን በተለየ የቶተንሀም ተጫዋቾች የግል ጥረት ነው” ብሏል።

ይህን አስተያየት የሰሙት የቶተንሀም አሰልጣኝ አንሄ ፖስቴኮግሉ በሰጡት ምላሽ “በጣም ጥሩ። ዛሬ ምሽት ስታዲየሙ ሁሉንም ነገር ይናገራል” በማለት በሜዳ ላይ ለሚሰነዘረው ትችት ምላሽ እንደሚሰጡ አሳውቀዋል።

- Advertisement -
Latest news
- Advertisement -
Related news
- Advertisement -

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here