የዘንድሮው የውድድር ዓመት ለማንችስተር ዩናይትድ በፕሪሚየር ሊጉ እጅግ አስቸጋሪ እንደነበር ይታወቃል። አሰልጣኙም ይህንን በተደጋጋሚ ሲገልጹት ቆይተዋል።
ይሁን እንጂ ማንችስተር ዩናይትድ ይህንን አስከፊ ዓመት በዩሮፓ ሊግ ዋንጫ በማንሳት እንዲሁም ለሻምፒየንስ ሊግ ቀጣይ ተሳትፎውን በማረጋገጥ የተሻለ ፍፃሜ እንዲኖረው ትልቅ ዕድል አግኝቷል።
ይህ ማለት ማንችስተር ዩናይትድ ዩሮፓ ሊግን ማሸነፍ ክለቡን በሂደት እየገነቡ ላሉት አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም በርካታ ጥቅሞችን ያስገኛል።
ቀይ ሰይጣኖቹ ወደ ፍፃሜው ለመድረስ ተቃርበዋል፤ ሆኖም ዛሬ ምሽት ለፍፃሜው ካለፉ ከፊታቸው ጠንካራ ተጋጣሚ እንደሚጠብቃቸው ግልጽ ነው።
የሩበን አሞሪም ቡድን የፍፃሜውን ጨዋታ ካለፈ የሚጠብቀው ተጋጣሚ ቶተንሀም ወይም ቦዶ ግሊምት ይሆናል።