የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በቀጣዩ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ የሊጉን ሻምፒዮን ለሆነው ሊቨርፑል የክብር አቀባበል እንደሚያደርግ ይፋ አድርጓል።
የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው ለሊቨርፑል የክብር አቀባበል እንደሚያደርግ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አረጋግጠዋል።
ባለፈው ሳምንት ሌላው የለንደን ክለብ ቼልሲ በተመሳሳይ ለሊቨርፑል የክብር አቀባበል ማድረጉ ይታወሳል።
ሊቨርፑል የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ማረጋገጡን ተከትሎ ከአርሰናል በተጨማሪ ብራይተን እና ክሪስታል ፓላስም የክብር አቀባበል እንደሚያደርጉለት ይጠበቃል።