የሰማያዊዎቹ ዋና አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ተጨዋቾቻቸው ሻምፒየንስ ሊግ ለመግባት የሚፈልጉ ከሆነ በቀሪዎቹ ሁለት የሊግ ጨዋታዎች የግድ ማሸነፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ማሬስካ “ሻምፒየንስ ሊግ መግባት የምንፈልግ ከሆነ ቀሪዎቹን ሁለት ጨዋታዎች ማሸነፍ እንዳለብን በግልጽ አስጠንቅቄያለሁ” ብለዋል።
ኒውካስልን ከሜዳቸው ውጪ መጋጠም እጅግ ፈታኝ እንደነበር የገለጹት ማሬስካ በአስር ተጫዋች መጫወት ቀላል እንዳልነበርም አክለዋል። ሆኖም ቡድናቸው በሁለተኛው አጋማሽ የተፋላሚነት መንፈስ ማሳየቱን አመልክተዋል።
በተጨማሪም በጨዋታው ላይ ኒኮላስ ጃክሰን በቀይ ካርድ መባረሩ ቡድኑን ዋጋ እንዳስከፈለውና ተጫዋቾቹ ከዚህ ስህተት መማር እንደሚገባቸው አሳስበዋል።