የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ከቼልሲ ወጣት ግብ ጠባቂ ለማስፈረም በይፋ ጥያቄ ማቅረቡ ተዘገበ።
መድፈኞቹ ለ16 ዓመቱ የቼልሲ ግብ ጠባቂ ፍሬዲ ቤርናል 1.25 ሚሊዮን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ማቅረባቸው ተነግሯል።
ይሁን እንጂ ሰማያዊዎቹ ይህንን የዝውውር ጥያቄ ውድቅ ያደረጉ ሲሆን ወጣቱን ግብ ጠባቂ በቡድናቸው ውስጥ ማቆየት እንደሚፈልጉ ተገልጿል።
የእንግሊዝ ከ18 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ የሆነው ፍሬዲ ቤርናል በሌሎች ክለቦችም ከፍተኛ ፍላጎት እያሳደረበት እንደሚገኝ ተጠቁሟል።