የሊቨርፑሉ የፊት መስመር ተጫዋች ሉዊስ ዲያዝ በክለቡ ውስጥ ስላለው ደስታ በግልጽ ተናገረ።
ዲያዝ “በሊቨርፑል ለረጅም ጊዜ መቆየት እፈልጋለሁ” ብሏል። የኮንትራት ሁኔታውም በክለቡ አመራሮች በደንብ እንደሚታይና መፍትሄ እንደሚያገኝ ተስፋ እንዳለው ገልጿል።
“በጣም የተረጋጋሁና ደስተኛ ነኝ፤ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እየተደሰትኩ ነው” ሲልም አክሏል።
በተጨማሪም “እዚህ ከመጣሁበት የመጀመሪያው ቀን ጀምሮ በዚህ ትልቅ ክለብ እግር ኳስ በመጫወት ደስተኛ ህይወት እየኖርኩ ነው” ሲል ያለውን ስሜት ገልጿል።