የኦሎምፒክ ሊዮኑ የፊት መስመር ተጨዋች ራያን ቼርኪ በሚቀጥለው ዓመት ክለቡን ለመልቀቅ ያለውን ፍላጎት በይፋ አስታውቋል።
ተጫዋቹ በመግለጫው “በእግር ኳስ ሕይወቴ ውስጥ አዲስ ፈተና ለመጋፈጥ ዝግጁ ነኝ” ብሏል። እንዲሁም በክለቡ ውስጥ ለነበሩት ሁሉ ምስጋናውን አቅርቧል።
ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጫዋች ራያን ቼርኪ ከአሁኑ ክለቡ ኦሎምፒክ ሊዮን ጋር ያለው የውል ማፍረሻ ዋጋ 22.5 ሚሊዮን ዩሮ እንደሆነ ተገልጿል።