የማንችስተር ሲቲው ኮከብ ተጫዋች ኬቨን ዴ ብሩይን ስለወደፊት ክለቡ እያሰበ መሆኑን ገለጸ። “ስለወደፊት ህይወቴ ከክለቦች ጋር እየተነጋገርኩ ነው፣ አዎ። የትም ብወስን ጥሩ እግር ኳስ መጫወት እፈልጋለሁ” ብሏል።
በእንግሊዝ መቆየት ይችል እንደሆነ ሲጠየቅም “ማን እንደሚመጣ ይወሰናል… ቤተሰብ፣ ልጆች አሉኝ፣ ለሁላችንም የሚስማማ ውሳኔ መወሰን አለብኝ። ውሳኔው ቀላል አይደለም” ሲል ምላሽ ሰጥቷል።