የኒውካስል ዩናይትድ አማካይ ተጫዋች ብሩኖ ጉማሬሽ ቡድናቸው የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ የማንሳት አቅም እንዳለው ተናግሯል።
“መቼ እንደሆነ በትክክል አላውቅም፣ ነገር ግን ፕሪሚየር ሊጉን ማሸነፍ እንደምንችል በእርግጠኝነት አምናለሁ” ሲል ጉማሬሽ አስተያየቱን ሰጥቷል።
“አንድ ዋንጫ ብቻ በቂ አይደለም” ያለው ብራዚላዊው አማካይ በቀጣይነትም ቡድኑ ብዙ ዋንጫዎችን የማንሳት አቅም እንዳለው ገልጿል።
በተጨማሪም “ሶስት ወይም አራት ተጫዋቾችን በአዲስ መልክ ካስፈረምን ክለቡ በትልቁ ደረጃ ተፎካካሪ መሆን ይችላል” ሲል ተናግሯል።