የፈረንሳዩ ክለብ ፓሪስ ሴንት ዠርሜን (ፒኤስጂ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ካሸነፈ ታላቅ የጎዳና ላይ የድል በዓል እንደሚያዘጋጅ ታውቋል። ይህ ታሪካዊ ክብረ በዓል በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ በሚገኘው ታዋቂው “Champs-Élysées” ጎዳና ላይ እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ከዚህም ባሻገር፣ ፒኤስጂ የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫውን ካነሳ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለቡድኑ አቀባበል ሊያደርጉ እንደሚችሉ ተነግሯል።