የ2024/25 የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት በፖላንድ፣ ቭሮትስዋፍ በሚገኘው ስታዲየም ቭሮትስዋፍ በቼልሲ እና በሪያል ቤቲስ መካከል ይካሄዳል። ጨዋታው በአዲስ አበባ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት 4:00 ላይ ይጀምራል።
ይህ የፍጻሜ ፍልሚያ ለሁለቱም ክለቦች የመጀመሪያው የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ የፍጻሜ ተሳትፎ ሲሆን፣ በተለይ ለሪያል ቤቲስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ውድድር ፍጻሜ የደረሰበት አጋጣሚ ነው። ቼልሲ በታሪክ አስራ ሶስት ጊዜ ለተለያዩ የአውሮፓ ዋንጫዎች ፍጻሜ መድረስ ችሏል።
በአሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ የሚመራው ቼልሲ ዋንጫውን ለማንሳት ትልቅ ግምት የተሰጠው ቢሆንም፣ በዚህ የውድድር ዓመት ሪያል ማድሪድ፣ አትሌቲኮ ማድሪድ እና ፊዮረንቲናን የመሳሰሉ ጠንካራ ቡድኖችን የረታው ሪያል ቤቲስም በቀላሉ የሚታይ ቡድን አይደለም። ዛሬ ምሽት በአውሮፓ መድረክ አዲስ ታሪክ የሚጻፍ ይሆናል።