የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ የፍጻሜ ተፋላሚዎች የሆኑት ቼልሲ እና ሪያል ቤቲስ በዛሬው ዕለት ለ5ኛ ጊዜ እርስ በርስ የሚገናኙ ሲሆን፣ የአውሮፓ መድረክ ግንኙነታቸው ከሃያ ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ነው።
መረጃዎች እንደሚያሳዩት ሁለቱ ክለቦች ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት በ2005/06 የውድድር ዘመን የቻምፒየንስ ሊግ የምድብ ጨዋታዎች ላይ ነበር። በወቅቱ የተደረጉትን ሁለት ጨዋታዎች ሁለቱም ክለቦች በየሜዳቸው በማሸነፍ ነጥብ መጋራት ችለዋል።
ከዚያ በፊት ቼልሲ እና ሪያል ቤቲስ ሁለት ጊዜ ተገናኝተው ነበር፤ በዚያን ጊዜ “ሰማያዊዎቹ” ሁለቱንም ጨዋታዎች በማሸነፍ የበላይነታቸውን አሳይተዋል።