የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ የኤሲ ሚላኑን ግብ ጠባቂ ማይክ ሜኛንን ለማስፈረም የዝውውር ጥያቄ ማቅረቡ ተገለጸ።
ጣሊያናዊው ታዋቂ ጋዜጠኛ ፋብሪዝዮ ሮማኖ እንደዘገበው፣ “ሰማያዊዎቹ” ለፈረንሳዊው ግብ ጠባቂ ዝውውር 15 ሚሊዮን ዩሮ የዝውውር ሂሳብ አቅርበዋል። ማይክ ሜኛን ቼልሲን ለመቀላቀል ፍላጎት እንዳለው ከዚህ ቀደም ሲነገር ቆይቷል።
አሁን ላይ የዝውውር ሁኔታው በኤሲ ሚላን እጅ ውስጥ ሲሆን፣ ቼልሲ የአለም ክለቦች ዋንጫ ዝውውር መስኮት ማክሰኞ ከመዘጋቱ በፊት ከሚላን ምላሽ እንደሚፈልግ ተጠቁሟል።