ማንቸስተር ሲቲን የተቀላቀለው የኔዘርላንድ አማካይ ቲያኒ ሬንደርስ በቀጣይ ከክለቡ ጋር ዋንጫዎችን ለማሸነፍ እንደሚፈልግ ተናግሯል።
ሬንደርስ በሰጠው አስተያየት፣ “ማንቸስተር ሲቲ ከአለም ምርጥ ክለቦች አንዱ ነው፤ እዚህ በመምጣቴ ደስተኛ ነኝ” ብሏል። አክሎም “ጋርዲዮላን የምከታተለው ከባርሴሎና ጀምሮ ነው፤ ማንቸስተር ሲቲ የአለም ምርጡ አሰልጣኝ አለው። አርአያዬ ደግሞ ሊዮኔል ሜሲ ነው” ሲል ገልጿል።
“እግር ኳስ ዋንጫ ስለማሸነፍ ነው” ያለው ሬንደርስ፣ “ማንቸስተር ሲቲ ውስጥ ዋንጫዎችን እንደማሸንፍ ተስፋ አደርጋለሁ” በማለት ምኞቱን ተናግሯል።