ሪያል ማድሪድ የአርጀንቲናው ክለብ ሪቨር ፕሌት የአጥቂ አማካይ ፍራንኮ ማስታንቱኖን ማስፈረሙን አስታውቋል። ሎስ ብላንኮዎቹ የ17 ዓመቱን ተስፈኛ ተጫዋች ለስድስት ዓመታት የሚያቆይ ውል ሲያስፈርሙ፣ ተጫዋቹ በቀጣዩ ነሐሴ ወር ክለቡን እንደሚቀላቀል ተገልጿል።
ሪያል ማድሪድ ለወጣቱ ማስታንቱኖ በሪቨር ፕሌት ባለው ውል ውስጥ የነበረውን 45 ሚሊዮን ዩሮ የውል ማፍረሻ ከፍሏል። ይህ ዝውውር ተጫዋቹ በኤንዞ ፈርናንዴዝ ተይዞ የነበረውን የክለቡን ከፍተኛ የሽያጭ ሪከርድ (44 ሚሊዮን ዩሮ) ማሻሻል ችሏል።