የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሀም ፈረንሳዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ማቲያስ ቴልን በቋሚነት ማስፈረሙን አስታውቋል። ማቲያስ ቴል ግማሽ የውድድር ዓመቱን በቶተንሀም በውሰት ያሳለፈ ሲሆን፣ አሁን ላይ በቋሚነት ለክለቡ ፈርሟል።
ቶተንሀም ተጫዋቹን ለማስፈረም 35 ሚሊዮን ዩሮ የከፈለ ሲሆን፣ ቀጣይ በሚጨምሩ 10 ሚሊዮን ዩሮዎች ጭምር የዝውውር ዋጋው ይጨምራል። የ19 ዓመቱ የፊት መስመር ተጫዋች ማቲያስ ቴል በቶተንሀም ቆይታው 19 ጨዋታዎችን አድርጎ ሶስት ግቦችን ሲያስቆጥር፣ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫንም ማሳካት ችሏል።